About Us

እኛ ለኛ በስደት የተቋቋመው ሊባኖስ ሀገር ውስጥ ባሉ የቤት ሰራተኞች ነው። ተቋማችን የሚንቀሳቅሰው ማሕበረሰቡን ባማከሉ የሴቶች መብት ተሟጋች በሆኑ አክቲቪስቶች ሲሆን ትኩረት የሚያደርገው በድህነት ውስጥ ካሉ ሀገራት ወደ መካከለኛው ምስራቅ ተሰደው በቤት ውስጥ በሚሰሩ ሴቶች ጉዳይ ላይ ነው። በተለይም ሊባኖስ እና ኢትዮዽያ ሀገራት ባሉ ጉዳዮች ላይ ልዩ ትኩረት ይሰጣል። በስደት ላይ ያሉ የቤት ሰራተኞች በየእለቱ ለሚያጋጥሟቸው ችግሮች ሁለንተናዊ መፍትሔ እንሰጣለን። የምንሰጣቸው አገልግሎቶች ሕጋዊ፣ የመኖርያ ቤት እና የምግብ ድጋፍ፤ እንዲሁም የመጠለያ ድጋፍ አና የህክምና አገልግሎት ሪፈራል ወይም ምልከታ መስጠት፤ የሙያ ስልጠና መስጠት እና ወደ ሀገር ቤት ለመመለስ እና ወደ ማሕበረሰቡ ለመቀላቀል የሚያስችሉ ድጋፎችን ማድረግ ነው።

ተልዕኳችን

እኩልነት፣ ብቃት/ብርታት (ኢምፓወርመንት)እና ፍትሕ በቀድሞ እንዲሁም በአሁኑ ጊዜ በሊባኖስ እና በለሎች የመካከለኛ ምስራቅ ሀገራት ላይ በስደት ላሉ የቤት ሰራተኞች። እገዛ የሚፈልጉ በስደት ያሉ የቤት ሰራተኞችን በመደገፍ እንዲሁም በማሕበረሰቦቻችን ውስጥ ያሉ ታዳጊ እና አዋቂ ሴቶችን በማበረታታት እና በማብቃት የካፋላ ስርዓትን ለማስወገድ የሚያስችሉ ማሕበረሰባዊ እንቅስቃሴ የመፍጠር አስተዋጽዖ እናደርጋለን። ይህንንም የምናደርገው ግንዛቤ በማስጨበጥ እና ሴቶችን በመደገፍ እንዲሁም መብታቸውን እንዲገነዘቡና እና እንዲያውቁ በማድረግ ነው።

ራዕያችን

ልዩነቶችን የሚቀበል፣መድሎዎ፣ በደል እና ብዝበዛ የሌለበት፤ እንዲሁም በስደት ያሉ የቤት ሰራተኞች መብትና በራስ የማድረግ እና የመወሰን አቅም መሉ በሙሉ የሚከበርበት እና የሚበረታታበት ማሕበረሰብ ማየት።

THE TEAM

ETHIOPIAN | WOMEN | DOMESTIC WORKERS ACTIVISTS
Engna Legna Banchyi
Banchi Yimer
Founder
Engna Legna Tsigereda
Tsigereda Brihanu
Projects Director
Engna Legna Messi
Genet Lema
Activities Coordinator
Engna Legna Mekdes
Mekdes Ylma
Director of Finance

FAQ




ማነው መድልዎ እየተደረገበት ያለው?

ሁሉም በስደት በሊባኖስ ውስጥ ያሉ የቤት ሰራተኞች እንዲሁም ከመካከለኛው ምስራቅ ከስደት ተመልሰው በኢትዮዽያ የሚኖሩ ሴቶች።

የትኛው መብት ነው እየተጣሰ ያለው?

Labor - forced confinement - health - liberty and security of person (rape-forced abortion) - - access to justice freedom of movement (trafficking).

መድልዎ በምን መልኩ ነው እየደረሰ ያለው?

Kafala system that privileges the sponsor - lack of accountability, justice and protection for MDW vs. sponsors, agencies, insurance agencies (profiteers) - guilty until proven innocent; no due process - exclusion from labor law. More populous, underage girls, language barriers, low education => added discrimination

ምን አይነት ለውጥ እንዲኖር ይፈልጋሉ?

ሊባኖስ፥: Abolish kafala - fair, protective system free of impunity - laws to protect MDW.

ኢትዮዽያ፥: Child trafficking stopped - awareness/ transparency, enforcement of laws targeting human traffickers and abusers.

ማህበረሰባቹ እንዴት ተጠቃሚ ይሆናል?

ሊባኖስ፥ ራስን ማጥፋት፣ የነፍስ ግድያ እና የአካል/የስነ-ልቦና ጉዳቶችን ይከላከላል። ፍትሕ የማግኘት መብት ይረጋገጣል፤ ከአደጋ እና በደል ነፃ የሆነ የስራ አካባቢ እና ሁኔታ በስደት ላሉ የቤት ሰራተኞች ይፈጠራል፤ ኤጀንሲና ስፖንሰሮች በስደት በሊባኖስ ባሉ የቤት ሰራተኞች ላይ ያላቸው ሙሉ በሙሉ የሆነ የበላይነት እና ተቆጣጣሪነት ይቆማል፤ በነፃነት የመንቀሳቀስ መብት ይረጋገጣል፤ በስደት ያሉ የቤት ሰራተኞች ድምፅ ይኖራቸዋል፤ በመካከለኛው ምስራቅ ያሉ ስደተኛ የቤት ሰራተኞችን ከፆታዊ ትንኮሳ እና ጥቃት እንዲሁም በዘረኝነት ላይ ከተመሰረቱ ጥቃቶች እና መገለል ከለላ ያገኛሉ።

ኢትዮጵያ፥ በኢኮኖሚ ራስን መቻል፤ በኢትዮጵያ ከመካከለኛው ምስራቅ ተመልሰው ያሉትን በገንዘብ አያያዝ እና አጠቃቀም ዙሪያ ብቃት፤ በወንድ የቤተሰብ አባላት ከሚደርስ መድልዎ እና የገቢ መነጠቅ ጥበቃ

በሰዎች መካከል ያለው ግንኙነት እንዴት ይቀየራል?

ሊባኖስ፥ የአሰሪ እና ሰራተኛ ግንኙነት፤ በግል ህይወት ውስጥ ጣልቃ አለመግባት እና ከስራ ጋር ያልተያያዙ የሰራተኛ የህይወት ክፍሎች ላይ ቁጥጥር ማቆም፤ ሰብዓዊነት እንደሌለው እንደ እቃ ሰዎችን ማየት ማቆም፤ ደሞዝ፣ የጤና አገልግሎት እና በነፃነት የመንቀሳቀስ መብቶች ይረጋገጣሉ።

ኢትዮዽያ፥መድሎን መቀነስ፣ የበለጠ ርሕራሔ ማሳያት፣ በስደት ያሉ ወይም የነበሩ የቤት ሰራተኞችን እንደ ገንዘብ ምንጭ ብቻ ማየት ማቆም፣ ለሰራተኞች ህጋዊ ጥበቃ ማድረግ

ምን ነገሮችን ብታዩ፣ ብትሰሙ፣ ቢሰማቹ ወይም በህይወት ልምዳቹ ብታሳልፉ ነገሮች እንደተለወጡ ታውቃላቹ?

የአጠቃላይ የማህበረሰቡ የአስተሳሰብ እና የባሕሪ ለውጥ፣ የሰራተኛ እና አሰሪ ህጎች መከበር፣ ፍትሐዊ ያልሆነውን ስርዓት ከለላ አድርጎ ብዝበዛ አለማረደግ

የትኞቹ የሰብዓዊ መብቶች እውቅና ያገኛሉ ወይም በሰዎች ተጠቃሚ ይሆናሉ?

Labor - health - liberty and security of person (rape-forced abortion) - freedom of movement (trafficking) - access to justice - self-determination/ agency.

amAmharic